ወዳጄ መቼም ከትምህርቱ አለም ተመርቀው የወጡ ከሆነ የስራ ፍለጋን ነገር ጠንቅቀው እንደሚያውቁት እርግጠኛ ነኝ፡፡ እናም ምናልባት ይሄን የስራ ቅጥር ነገር ማስታወቂያዎችን እየተከታተሉ አመልክተው ተቀጥረው እንደሁ፤ ወይ ደግሞ አሁንም በመሞከር ላይ ከሆኑ በእስከዛሬው ልምድዎት እንደው በዛ ቢባል ስንት ሰው ተፈልጎ ከስንት ሰው ጋር ተወዳድረው ይሆን? ትዝታዎችዎትን ወደ ኋላ መለስ ብለው ማሰላሰልዎትን ለኋላ ያቆዩትና “ምን ቁጥሩ ቢበዛ በተአምር ለአንድ ስራ ከሚሊየን ሰዎች ጋር ተወዳድረው አያውቁም! ህንዳዊ ካልሆኑ በስተቀር!” የሚል የሚመስለውን የቢቢሲ መረጃ እኔ ልንገርዎት፡፡
የስራ አጥነት ችግር ክፉኛ በተንሰራፋባትና በአስር ሚሊየኖች የሚቆጠሩ
ነዋሪዎቿ ስራ አጥ በሆኑባት የህንዷ ኡታር ፕራዴሽ ግዛት፤ መቼም የቸገረው እርጉዝ ያገባል እንደሚባለው ሆኖ ሳይሆን አይቀርም፤
ታዲያ እነዚህ ዶክተሮችና በተለያዩ ደረጃዎች የሚገኙ ምሩቃን ሳይቀሩ የተወዳደሩበት ይህ ስራ እድሉን አግኝቶ ለሚቀጠር አንድ
ግለሰብ የሚያስገኘው የወር ገቢ በህንድ ገንዘብ ሩፒ 16 ሺ፤ ወደ ብር ስንመልሰው ደግሞ 4800 ብር ገደማ ብቻ ነው፡፡
እናልዎት ወዳጄ “እነዚህን 2 ሚሊየን 300 ሺ ስራ ፈላጊዎች አወዳድሮ
ለመቅጠር ምን ያክል ጊዜ ይሆን የሚፈጀው?” የሚል ጥያቄ መነሳቱ አልቀረምና በጉዳዩ ላይ የተጠየቁት የመስሪያ ቤቱ ከፍተኛ የስራ
ሃላፊ አቶ ፕራባት ሚታል ለቢቢሲ ሲመልሱ… “ያው አመልካቾቹን ቃለ መጠይቅ ነው የምናደርግላቸው… እናም እያንዳንዱን አመልካች
ቃለ መጠይቅ አድርገን እንጨርስ ብንል 4 አመታት ሳይፈጅብን አይቀርም!” ነው ያሉት፡፡ ታዲያ ይህም የሚሆነው 10 ቃለ መጠይቅ
አድራጊዎች ተመድበው በአንድ ቀን 2 መቶ አመልካቾችን ቃለ መጠይቅ እያደረጉላቸው፤ በወር ለ25 ቀናት ከሰሩ እንደሆነም ነው
ሀላፊው ያስረዱት፡፡
ወዳጄ እንግዲህ ምናልባት ነገሩን በሌላ መልኩ እንየው ካልን መስሪያ ቤቱ ላወጣው
ክፍት የስራ ቦታ - እንደነ ጅቡቲ፣ ሌሴቶ፣ ጊኒ፣ ቦትሱዋና፣ ናሚቢያና ጋቦንን የመሳሰሉ የአፍሪካ ሀገራትን ጨምሮ ሌሎች ከመቶ
በላይ የሚደርሱ፤ የህዝብ ብዛታቸው 2.3 ሚሊየን የማይሞላ፤ ሀገራት ከያዙት - ከአንድ ሀገር ሙሉ ህዝብ በላይ ነው ቅጠረኝ
ሲል ማመልከቻውን ያስገባው፡፡
ታዲያ ምናልባት ለቃለ መጠይቅ እድሉ ቢሰጠው አንድ ሰው ዛሬ ላይ ላስገባው
ማመልከቻ ከአራት አመታት በኋላ ሊሆን ይችላል ቀጠሮው የሚደርሰው፡፡ ሊያውም ከአንድ ሀገር ሙሉ ህዝብ ቁጥር በላይ ከሆነ ስራ
ፈላጊ ጋር ሊወዳደር ማለት ነው፡፡ ከዚህ ሁሉ ግን አራት አመት ለመቀጠር ከመጠበቅ ስራ ለመፍጠር ቢታትር አንድ ሰው የተሸለ
ገቢ የሚያገኝበትን ስራ የሚፈጥር አይመስልዎትም ወዳጄ፡፡
ዳንኤል
ቢሠጥ
ለአዲስ
ቴሌቪዥን እና ለኤፍ ኤም 96.3
No comments:
Post a Comment